Skip to main content

Posts

Showing posts from January 15, 2023

General Biology Unit 1: Introduction, discovery, and types of #Cell

 

አጼ ዘረያእቆብ

  አጼ ዘረያእቆብ በአንድ ወቅት በዘመናቸው ላሉት ሰዎች እንዲህ ብለው ነበር ፥ "አስመ ጽሙአን ለትምህርት ብሄረ ኢትዮጵያ ሄራን" "ምርጦቹ የኢትዮጽያ ሰዎች ትምህርትን የተጠሙ ናቸው።" ይህ ንጉስ አንድ ሰው በአቅራቢያው ቢማር በሃዘኑም በደስታውም ከቤተሰብ ጋር ሲያሳልፍ ለትምህርቱ ሙሉ ጊዜውን አይሰጥም ብሎ በማሰብ ወደ ሌላ ቦታ በመሄድ የአብነት ትምህርት እንዲማሩ አድርጓል፣ በዘመናችን እስኮላር ሽፕ እንደሚባለው ማለት ነው። ታድያ በአሁኑ ጊዜ ይሄ ንጉስ ቢኖር ኑሮ እንዲህ የሚል ይመስለኛል!! <አስመ ጽሙአን ለፖለቲካ ብሄረ ኢትዮጽያ ሄራን> ምርጦቹ የኢትዮጽያ ሰዎች ፖለቲካ የተጠሙ ናቸው።

አፍሪካዊው ቶማስ ፉለር እና ካልኩሌተር

በአውሮፓዊያን ባሪያ ተብሎ የተጠራው አፍሪካዊ የሂሳብ ሊቅ የማሰብ ችሎታው ነጮችን ያስደነገጠ እና አፍሪካዊያን እንደነሱ እኩል ማሰብ ብቻ ሳይሆን የተሻለ ማሰብና መስራት እንደሚችሉ ያዩበትና የተረድበት ነበር። በ1724 በ14 ዓመቱ ለባርነት የተሸጠው አፍሪካዊው ቶማስ ፉለር አንዳንድ ጊዜ በጭንቅላቱ ውስጥ ያሉ ውስብስብ የሂሳብ ስሌቶችን የመፍታት ልዩ ችሎታ ስላለው “ቨርጂኒያ ካልኩሌተር” ተብሎ ይጠራ ነበር። በአንድ ዓመት ተኩል ውስጥ ምን ያህል ሴኮንዶች እንደነበሩ ተጠይቆ በሁለት ደቂቃ ውስጥ 47,304,000 ብሎ መለሰ. አሁንም አንድ ሰው 70 አመት ከ17 ቀን ከ12 ሰአት እድሜ ያለው ስንት ሰከንድ እንደኖረ ሲጠየቅ በአንድ ደቂቃ ተኩል 2,210,500,800 ብሎ መለሰ። ከሰዎቹ አንዱ ስሌቶችን በወረቀት ላይ እየሠራ ነበር, እና መልሱ በጣም ቶሎ ስለመለሰ እና ትንሽ ስለሆነ ፉለር ተሳስቷል. ፉለር በችኮላ መለሰ ይሉት ነበር፡- ነገር ግን እነሱ (ነጮች) ጷግሜን በነሱ (leap year) ብለው የሚጠሩትን እረስተው ነበር። ስለሆነም የጷግሜን ወር ታሳቢ ተደርጎ ሲሰላ ድምሩ ትክክል ይመጣ ነበር። ምንጭ: ጥቁር ታሪክ-ጃክ ኪንግ

ስራ ሂወት መሆኑን #ተማርኩና ኑሮየን #ማቅናት ቻልኩ:-

ከንቲባ ገብሩ ተብለው ከመጠራታቸው በፊት ጎባው ደስታ በመባል ይታወቁ ነበር። ከንቲባ ገብሩ የጎንደር ከንቲባ ነበሩ። አንድ ቀን እንዲህ ብለው ነበር ኢየሩሳሌም ሄድኩና ትምህርት ቤት እንደገባሁ ሰሞን ከተማሪዎች ጋር የደረቀ ፍግ በአካፋ እየዛቅን በሚገፋ ጋሪ ወደ የአትክልቱ እንድናደርስ ታዘዝን ተማሪዎች የለመዱት ስራ ስለነበረ እየተዝናኑና እየተጫወቱ ይሰራሉ። የክፍል አለቃችን መጣና ጎባው (የገብሩ ቅጥል ስሙ ነው) አትሰራም እንዴ? ቢለኝ እኔ ፍግ ለመዛቅ አልመጣሁም ለመማር እንጅ ብየ መለስኩለት። የክፍሉ አለቃም ይህን ሂዶ ለዋናው አስተዳደር ነገራቸው። እሳቸውም ተወው ግድ የለም #አሱ #የመጣው #ስራ #መስራት #ካለመዱ #ሃገር ስለሆነ አስኪላመድ ድረስ አትንኩት ብለው ሲናገሩ ሰማሁ። እኔም ትቂት ደቂቃዎች ከቆየሁ በኋላ ቆጨኝና የሚገፋውን ጋሪና አካፋየን ይዠ እንደ ጓደኞቸ እየተሻማሁ መስራት ጀመርኩ። ከዚያ በኋላ ስራ ሂወት መሆኑን ተማርኩና ኑሮየን ማቅናት ቻልኩ። ??? እስኪ እራሳችንን እንመልከት እኔ፣ አንች። እኛና እናንተ ስራ እንወዳለን ዝቅ ብለን እንሰራለን ወይስ ሌሎች ሲሰሩ እናሾፋለን፣ ሰበበኞች ነን፣ ወደኋላ እንጎትታለን፣ ጓደኛ መስለን እሾህ እንሆናለን? እስኪ የትኛው ባህሪ እንዳላችሁ መልሱልኝ??? በርግጥ አንተ ማነህና ማንን ትጠይቃለህ ብትሉኝ ቀና ሰው ፍለጋ ብየ እመልሳለሁ።

#ሎሬት #ጸጋየ #ገ/መድህን

እንዲህ ይላል፦ ጥበብ ይናፍቀኛል ተቻችሎ የሚኖር ህዝብ ያስቀናኛል ድንቁርና ያስፈራኛል ጦርነት ያስጠላኛል ጸጋየ በ 13 አመቱ “የዳዩናሲስ ዳኝነት” የተሰኘውን ድርሰት ዳግማዊ አጼ ሀ/ስላሴ አምቦን ሲጎበኝ ይህንን ድርሰት አቅርቦ ንጉሱም በጣም ስለወደዱት የእጅ ስሃታቸውን ሸልመውታል። በደርግ ዘመን ደግሞ ኢ.ሳ,ፓ.አ.ኮ. ጽ/ቤት በተሰጠው ትዛዝ፡ መሰረት ሙስናን ለማስወገድ የኪነ ጥበብ ሰዎች ከቁጥጥር ኮማሽን ጋር በመሆን የሙያቸውን ሚና እንዲጫወቱ ተጠይቀው ወደ ጽ/ቤቱ ከተጠሩት መካከል አንዱ ሎሬት ጸጋየ ገ/መድህን ነበር። ጸጋየ በስብሰባው እንዲህ ብሎ አስተያየት ሰጠ “ #እናንተ #እኮ #እኛን #ሌባን #ሻይ (ሌባ አፈላላጊ) #አደረጋችሁን #ችግሩ ግን #ሌባ #ሻዩን #የሚሰደው #ሌባው #መሆኑ ነው።” በማለት የነበረውን አመራር እርሱ ያለበትን ሁኔታ ከእውነታው ጋር አለመመሳከሩን ፊት ለፊት ተናገር። አሁንስ????????

General Microbiology Unit 2 (Part 3)- Pure culture techniques

 

General Microbiology Unit 2 (part1): Methods in microbiology (#Microbial_growth_control)

 

General Microbiology Unit 1- Introduction and History of Microbiology

 

Grade 11 Biology Unit 2 (Part 1): Inorganic and organic molecules

 

Grade 11 Biology Unit 2 (Part 2): Inorganic molecule (#Water)

 

Grade 11 Biology Unit 2 (Part 4): Organic molecules (#Lipids)

 

Grade 11 Biology Unit 2 (Part 3): Organic molecules (#Carbohydrate)

 

ኢትዮጵያዊያን #ሲስፊስ ሆን እንዴ?

እኔ እጠይቃለሁ?? ሲስፊስ በግሪክ አፈ ታሪክ ውስጥ በአማልክት መርገም የተፈረደበት ሰው ነበር። ፍርዱም ትልቅ ቋጥኝ ከተራራው ጥግ አንስቶ ወደ ተራራው ጫፍ ማውጣት ነበር። ቋጥኙን ከጥግ አንስቶ ወደ ተራራው ጫፍ ሲደርስ ተንከባሎ ወደ ነበረበት እየተመለሰ ማብቂያና መቋጫ የሌለው ስራ፣ ውጤት የሌለው ተግባር ያከናውን ዘንድ የተፈረደበት ሰው..... እኛም ከዚህ የተለየ እጣ ፋንታ ያለን አልመስልህ አለኝ ዛሬ ዛሬ እርጥቡ ነደደ፣ ዉሃ ሽቅብ ፈሰስ፣ አታላዮች በዙ፣ ትልቅ ሰው ጠፋ ስለሆነም ብዙዎች አባቶቻችን እየረገሙን ሞቱ፣ እያወገዙን ወደ መቃብር ወረዱ፣ እርግማናቸውን በጋቢያችን ዘርግተን ተቀበልናቸው። የሰዎች ጊዜ ከጀንበሯ ጋር አብሮ የጠለቀ ይመስላል ግን አንድ ነገር እርግጠኛ ነኝ ጸሃይ መውጣቷ እንደማይቀረው ሁሉ መልካሙ ጊዜም መምጣቱ አይቀርም ግን እስከሚያልፍ ያለፋል። #ሳጥናኤል #ከክብሩ #የተዋረደው #ልፍጠር ብሎ #በፈጣሪ #ስራ #ስለገባ እንጅ #የአምላክን #የእጅ - ስራ / #ፍጡር #ሲያፈርስ ተገኝቶ አይደለም። በዚህም የተነሳ በአሁኑ ጊዜ ከሳጥናኤል እንደበለጥን ይሰማኛል። ወፎች እንኳን አውቀው ጎጆ ሲቀልሱ እኛ ብቻ ቀረን ተባልተን እርስ በእርሱ መዝጊያ፦ "ኢዮሃ ድጋ ለሀገር ዘእንበለ አሐዱ ሄር" "ከአጥቂ ጋር የሚያጠቃ እሱ እርካሽ ነው።" አምላክ ነፍሳችሁን በአጸደ ገነት ያኑረው!!!

ቄስ እና መርጌታ

አንድ ቄስ እና መርጌታ በመካከላቸው አለመግባባት ይፈጠራል። በዚህም ጉዳይ ቄሱ መሪጌታውን በሰው ፊት እውቅት የሌለው እደሆነ ለማሳየት አሰቡ ነገር ግን በእውቀት እንደማይደርሱበት ተገነዘቡ። ኖም ግን አንድ ቀን ሰዎች ይሄ መሪጌታ አይችልም፣ እውቀት የለውም መሪጌታ ማለት እነ እከሌ እያለ የሌላ መሪጌታ ስም መጥራት ጀመረ በመቀጠልም ይህን ለማረጋገጥ አንድ ጥያቄ ልጠይቀው ነው ይህንን ከመለሰልኝ እኔ እቀጣለሁ አለ። ለመሪጌታው እንዲህ ሲል ጠየቀው “እንዳይ” ማለት ምን ማለት ነው? አለው። መርጌታውም “እንጅ” ብሎ መለሰ ቄሱም ቶሎ ብሎ ሰማችሁት አይደል ይሄው ምንም አያቅም አላቸው። ግን እንዳይ የግዕዝ ቃል ሲሆን በአማርኛ “እንጃ” ማለት ነው። ቄሱ የተሰበሰቡት ሰዎች ግዕዝ ስለማያቁ ነበር በነሱ ዘንድ እንደ አላዋቂ እዲቆጠር የሞከረው። አሁንም በኛ ጊዜ መጀመሪያ የማያውቅ፣ የማያስተውል፣ የማይጠይቅ ትውልድ እንዲፈጠር ከላይ እስከታች የቻሉትን አደረጉና በመጨረሻም ይህ የምናየው ሰቆቃ ተፈጠረ። ፍቅር በሚዲያ የተለያየ እምነትና አስተሳሰብ ያላቸውን ሰዎችን አብረው ፎቶ እያነሱ ፖስት ማድረግ ብቻ ሆነ ግን ህያው የሆነ ፍቅር ጠፋ። በጥላቻ ተሞልቶ ፍቅር ቢሰበክ ለሱ ምኑም አይደል።

#እፉኝት

         እፉኝት (አከድና) የሚባለው እባብ፦ ከእንብርታቸው በታች እስከ ጅራታቸው የአዞ መልክ አላቸው። ማሕጸን ግን የላቸውም ነገር ግን ሴቷ ከሃፍረቷ አካባቢ እንደ መድፌ ቀዳዳ ያለ ቀዳዳ አላት። ወንዱም ከእርሷ ጋር በተገናኘ ጊዜ ዘሩን በአፏ ያደርግባታል። እርሷም አባለ ዘሩን ትውጠዋለች። ወንዱም ወዲያውኑ ይሞታል። በጸነሰች ጊዜም የመውለጃ ብልት ስለሌላት ልጆቿ የእናታቸውን ማሕጸን ቀደው ይወጣሉ። በመወለዳቸውም እናታቸውን ይገድላሉ።

#በእጅ የያዙት #ወርቅ #ከመዳብም #ያንሳል

አንድሪ ሩሽ ይባላል የቀድሞው የአሜሪካ ሰራዊት/ጦር አባል ነበር። 23 አመት ካገለገለበት የአሜሪካ ጦር እራሱን በጡሬታ ያገለለው የ47 ዓመት አሁን ላይ እራሱን ጦሩ በማግለል በነጩ ቤተመንግስት /white house/ በሸፍነት ይሰራል። የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ከቢል ክሊንተን (Bill Clinton)፣ ጆርጅ ቡሽ፣ ባራክ ኦባማ፣ ዶላንድ ትራምፕ እነሱና ቤተሰቦቻቸው የሚመገቡትን ምግብ የሚሰራና አሁንም እየሰራ ያለ ሼፍ ነው አንድሪ ራሽ። በነጩ ቤተመንግስት /white house/ በሸፍነት የሸፎች አለቃም ሁኖ ሰርቷል። ከሸፍነቱ በተጨማሪ በአዕምሮ ጤና ተማጋችነቱና አነቃቂ ንግግሮቹ ይታወቃል። ይህ ሰው በሂወቱ ትልቅ ትርጉም የሚሰጠውን ምልክት በቀኝ ክንዱ ላይ በንቅሳት መልክ አስቀምጧል። የራሽ ቀኝ እጁ ላይ የሰፈረው የንቅሳት ጹሁፍ በአማርኛ “ #ኢትዮጵያ ” ይላል። አንድ ቀን እጅ ላይ ያለውን የአማርኛ ንቅሳት ትርጉም ሲያብራራ #የጥቁር #ህዝቦች #ኩራት የሆነችውን ሃገር ለማክበር በማሰብ ነው ብሏል። አለም ላይ ልክ እንደ ራሽ ያሉ ጥቁር ሰዎች የአሸናፊነት ምልክት የሆነውን ኢትዮጵያ የሚለውን ስም አንዳንዶቹ በጡንቻቸው ብዙወች ደግሞ በልባቸው አትመውታል። ለኛ ለኢትዮጵያዊያን ደግሞ “በእጅ የያዙት ወርቅ ከመዳብ እኩል ነው” ከሚለው አባባል እንኳን ወርደን “በእጅ የያዙት #ወርቅ #ከመዳብም ያንሳል” በሚል ብሂል በዘር በሃይማኖት በፖለቲካ ተከፋፍለን የነጻነት ቀንዲል የሆነችዋን ታላቋን አገር መቀመቅ ከተትናት። ለዚህ ደግሞ እኔም፣ አንተም፣ አንችም፣ እናንተም ሁላችንም ነን። ለታላቅነቷ ጠጠር እንደመወርወር ለመንገዳገዷ/ለድህነቷ/ መርግ ጣልንባት።

Could you accept or challenge him?

"There are no #Applied #Sciences .... but there are the #Applications of #Science ." Louis Pasteur

#ልብ እንደ #አእምሮ ማሰብ ይችላልን?

ኩላሊት (የምክር ዙፋን) እና ልብ (የጥበብ ዙፋን) ከአእምሮቻን (የእውቀት ዙፋን) በተጨማሪ ማሰብ ይችላሉ ወይም Center of intelligence በመባል ይታወቃል። አእምሮ ብቻውን ምንም መስራት አይችልም ሁለቱ ማንጠሪያዎች ናቸው የራሳቸው የሆነ የእውቀት ማንጠርና በራሳቸው ማሰብ የሚችሉ ናቸው። የሃገራችን እውቀት ብዙ ዘመናትን አስቆጥሯል (ኩላሊት የሚያጤሰው ልብ የሚያመላልሰው ናላ/አእምሮ የሚያወርሰው ይባላል) በነጮጭ ግን ልብ እንደሚያስብ የተደረሰው በ1991 G.C ነው። ልብ 40000 የተለያዩ ኒውሮን (sensory neuron) ሴል (little brain in the heart) አሉት ኩላሊትና አንጀት አካባቢ ደግሞ 500 ሚሊዮን ነውሮን አሉት (sensory neuron) ። እነዚህ ሴሎች ልክ እንደ አንጎላችን ማሰብ ይችላሉ የራሳቸውንም ውሳኔ መስጠት ይችላሉ። ሰለዚህ ልብ የራሱ ሚሞሪ አለው። ግርክ ብራደን ሁለት ምሳሌዎችን አቅርቧል፡ ምሳሌ 1:- አንዲት ሴት ነበርች እናም ልቧ በጣም ስለተጎዳ ሌላ በሞተር ሳይክል አዳጋ የተጎዳ የ አንድ ወንድ ሰው ልብ በቀዶ ጥገና ተቀየረላት። ካገገመች በኋላ ምን ምግብ ይምጣልሽ ብሎ ሆስፒታሉ የሚሰጠውን ምግብ ሲያቀርብላት አልበላም አለች። ምን ነው የምትፈልጊው ተብላ ስትጠየቅ KFC (በነጮች የታወቅ ብራንድ ምግብ ነው)። ይች ሴት ግን ይህንን ምግብ በሂወቷ በልታ አታቅም ይልቁንም በጭራሽ ይህንን ምግብ እንደማትወድ ታሪኳ ያስረዳ ነበር። በኋላ ይህ ጸባይ ለምን ተቀየረ ብላ ስታስብ ልብ የተቀየረላትን ልጅ ቤተሰቦች ማፈላለግ ጀመረ ከዛም የልጁን ታሪክ ቤተሰቦቹ እንዲነግራት ስትጠይቃቸው ልጁ በጣም ይወደው የነበረ ምግብ KFC ሆኖ አገኘችው። ስለዚህ የልጁ ሚሞሪ እሷ ጋር ቀርቷል ማለት ነው። ...

እንኳን አደረሳችሁ

  እንኳን ለጌታችን ለመድሃኒታችን #የኢየሱስ #ክርስቶስ #የልደት በአል አደረሳችሁ። በልደቱ የጥል ግርግዳ እንደተሰበር የዳቢሎስ ስራ እንደተጋለጠ ሁሉ ለሃገራችን ኢትዮጵያ የጥላቻ፣የዘረኝነትና የመከፋፈል ዘመን ማብቂያ ያድርግልን። በየቦታው ያሉትን ሴረኞችን ሴራቸውን ያክሽፍልን። ፍቅርና ጸጋውን ያብዛልን። መልካም የገና በአል 2015 ዓ.ም

Grade 11 Biology Unit 2 (Part 5): Organic molecules (#Protein)

 

Grade 11 Biology Unit 2 (Part 6): Organic molecules (#Nucleic_Acid)

 

Grade 12 Biology Unit 2 (Part 2): #Carbon #Nitrogen #Phosphorus & #Sulphur Cycles

 

Grade 11 Biology Unit 2 (Full Part): Biochemical Molecules

 

Grade 12 Biology Unit 2 (Part 3): Ecological succession

 

Grade 12 Biology Unit 2 (Part 4): #Biomes

 

Grade 12 Biology Unit 2 (Part 5): #Biodiversity

 

Grade 12 Biology Unit 2 (Part 6): #Population

 

Grade 12 Biology Unit 2: #Ecology (Full Part)

 

Grade 10 Biology Unit 1 (Full): Biotechnology

 

What is chromatin, nucleosome, and chromatin?

    and và conjunction cùng, và, với