Skip to main content

Posts

Showing posts from April 21, 2024

የሀሳብ ዕቁብ እንጣል

 #የሀሳብ_ዕቁብ_እንጣል ✍️ ብዙ ሰው ገንዘቡን ቆጥቦ ሕይወቱን ወደፊት ለማራመድ ሲል ከገቢው ቀንሶ፣ ከፍጆታው ቀምቶ እቁብ ይጥላል፡፡ ጥሩ ነው እቁብ መጣል፡፡ ብዙ ሰው ግን በገንዘቡ ዕቁብ አንደሚጥለው ሁሉ ማንነቱን ለማብሰል፣ ምንነቱን ለመረዳት፣ የሕይወት መንገዱን ለማደላደል፣ በራሱ ላይ ድልን ለመጎናፀፍ፣ የተሻለ ማንነት ያለው ሰው ለመሆን ሲል የሃሳብ ዕቁብ ሲጥል አይታይም፡፡  ✍️ ሃሳብ እንደገንዘብ የችግር ጊዜ ደራሽ ነው፡፡ አብዛኛው ሰው ችግሩን ለመፍታት የሚሞክረው በገንዘቡ ብቻ ነው፡፡ ገንዘብ ኖሮ ችግርን የሚቋቋም ጠንካራ ሃሳብ ከሌለ ዋጋ የለውም፡፡ የበሰለ ሃሳብ ኖሮ ገንዘቡ ባይኖር ብዙም ችግሩ አይባባስም፡፡ ሃሳቡ ችግርን መሻገሪያ ገንዘብን መፍጠር ይችላልና፡፡ የበሠለ ሃሳብ ከጨለማ ሕይወት የሚያወጣ ድልድይ ነው፡፡ አሻጋሪና ተሻጋሪ ሃሳብ መፍጠር የሚቻለው ቀድመን በጣልነው የሃሳብ ዕቁብ ነው፡፡ የተከማቸ ሃሳብ ዕውቀትን ይገነባልና፡፡    ✍️ ሰው ጤናማ ስሜት፣ የተረጋጋ ሕይወት፣ የበሠለ ማንነት፣ የሃሳብ ልዕልና እንዲኖረው ከዚህ በላይ ሃብት፣ ከዚህ በላይ የትምህርት ደረጃ፣ ከዚህ በላይ የስልጣን ሹመት፣ እንደዚህ ዓይነት ወዳጅና ቤተሰብ ሲኖረው ነው የሚል የተሠመረ ወይም የተቀመጠ መስመርም ሆነ ድምዳሜ የለም፡፡ ይሄን ሁሉ እውን እንዲሆን የሚያደርገው የሰው የገዛ ራሱ ሃሳብ ነው፡፡ ሃሳቡ ዕውቀት ሆኖ በተግባር ሲፈተን በየትኛውም ጊዜ ለሚደርስበት የኑሮ ውጣውረድ ችግሩን መፍቻ ቁልፍ ሆኖ ያገለግለዋል፡፡ ምክንያቱም ጤናማ ያልሆኑ ስሜቶችና የሕይወት ውሳኔዎች ጤናማ ካልሆነ ሃሳብና አመለካከት የሚመነጩ ናቸው፡፡  ✍️ ጤናማ አስተሳሰብን መፍጠር የሚቻለው ደግሞ ሰው ከሃሳቦቹ ጋር መጨዋወት፣ መሟገት፣ አልፎ ተርፎም ...

ክብር ለእናቶች

 ......እናትነት በአምፖል የፈጠራ ውጤቱ የምናውቀው ቶማስ አልቫ ኤድሰን አንድ ቀን ከትምህርት ቤቱ ወደ ቤት የተመለሰው መምህሩ የሰጠውን ወረቀት ይዞ ነበር፡፡ እናም ኤድሰን ለእናቱ እንዲህ አላት “መምህሬ ይሄን ወረቀት ለእናትህ ብቻ ስጣት ብሎ ሰጠኝ” በማለት ወረቀቱን አቀበላት፡፡ እናት እንባ በአይኖቿ ሞልቶ በወረቀቱ ላይ የሰፈረውን ሀሳብ ለልጇ አነበበችለት፡፡  ያነበበችለት ሀሳብም ይህ ነበር “ልጅሽ በአስተሳሰቡ ምጡቅ (ጀኒየስ) ነው፡፡ ይሄ ትምህርት ቤት ለእሱ አይመጥነውም። ለእሱ ብቁ የሆኑ መምህራኖችም ትምህርት ቤቱ የሌለው በመሆኑ እባክሽ አንቸው አስተምሪው ይላል” በማለት እንባዋን እየጠራረገች ወረቀቱን አጣጥፋ መሳቢያ ውስጥ ከተተችው፡፡ እናቱ ካረፈች ከብዙ ዓመታት በኋላ ኤድሰን በክፈለ ዘመኑ ካሉ የፈጠራ ውጤት ባለቤቶች አንዱና ቀዳሚው ከሆነ በኋላ አንድ ቀን እናቱ እቃዎቿን የምታስቀምጥበትን መሳቢያ ማገላበጥ ጀመረ፡፡ ባጋጣሚ የተጣጠፈች ወረቀት ከመሳቢያው ጠርዝ አካባቢ ተሰክታ ይመለከትና አንስቶ ከፈታት፡፡  ወረቀቱ ልጅ እያለ ከመምህሩ ለእናቱ  ብቻ እንዲሰጥ ታዞ የተሰጠው ወረቀት እንደነበር አውቋል፡፡ ከፍቶ ሲያነበውም ወረቀቱ ላይ የሰፈረው ሀሳብ እንዲህ ይላል “ልጅሽ የአእምሮ ችግር ያለበትና ዘገምተኛ ነው፡፡ ከዚህ በኋላም ወደ ትምህርት ቤቱ እንዲመጣ አንፈቅድለትም” ይላል፡፡ ኤድሰን ለሰዓታት ካለቀሰ በኋላ ድያሪውን ከፍቶ እዲህ ሲል ጻፈ “ቶማስ አልቫ ኤድሰን አእምሮው ዘገምተኛ የተባለ ልጅ ነበር፡፡ ነገር ግን በጀግናዋና በልዩዋ እናቴ የምእተ ዓመቱ ጂኔስ ሁኛለሁ፡፡ ክብር #ለእናቶች 

በኢትዮጵያ እስከ 3ኛ ክፍል ያሉ 56 በመቶ የሚሆኑ ተማሪዎች ምንም ዓይነት ቃላት ማንበብ እንደማይችሉ ተነገረ‼️

 በኢትዮጵያ እስከ 3ኛ ክፍል ያሉ 56 በመቶ የሚሆኑ ተማሪዎች ምንም ዓይነት ቃላት ማንበብ እንደማይችሉ ተነገረ‼️ የሀገር አቀፍ ፈተናዎች ኤጀንሲ "ኢትዮጵያ ታንብብ" በሚል ባዘጋቸው ጉባኤ ላይ ያከናወነውን ጥናት ይፍ አድርጓል። ጥናቱም በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ 401 ትምህርት ቤቶች ላይ የተደረገ መሆኑን የተገለፀ ሲሆን በጥናቱ የትግራይ ክልል አለመካተቱ ተነግሯል። የዚህ ጥናት ተሳታፊ የሆኑት የሀገር አቀፍ ፈተናዎች ኤጀንሲ የትምርት ምዘናና ምርምር መሪ ስራ አስፈፃሚ ዳይሬክተር ዶክተር ኢፍ ጉርሙ እንደተናገሩት 56 በመቶ የሚሆኑ የ2ኛ እና የ3ኘ ክፍል ተማሪዎች አንድም ቃላት ማንበብ እንዳልቻሉ ገልፀዋል። ይህ ቁጥር ከባለፉት አመታት ጋር ሲነፃፀር በመጠኑ መሻሻል አሳይታል የተባለ ሲሆን ከሁለት አመት በፊት የተደረገው ጥናት ምንም ማንበብ የማይችሉት 63 በመቶዎች እንደነበሩ ጠቁመዋል። ለዚህም እንደምክንያት የተቀመጡት መምህራን ከአምስቱ የትምህርት ቀናት አራቱን መምህራን ይፅፋሉ ተማሪዎች ይገለብጣሉ ምንም የማንበቢያ እድል አይሰጣቸውም ሲሉ ዶክተር ኢፍ ጨምረው ተናግረዋል። በሌላ በኩል 70 በመቶ መምህራን አዲሱን የስረዓተ ትምህርት ስልጠና አለመውሰዳቸው እና 75 በመቶ መፀሀፍ ለተማሪዎች አለመድረሱ ለችግሩ መባባስ እንደምክንያት ተቀምጧል። ኢትዮጵያ ንባብ በ1998 በዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ የተመሰረተ እና በ2002 ዓ.ም በኢትዮጵያ የተመዘገበ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ሲሆን የህጻናትን የማንበብ ባህል ለማሳደግ እና ለማዳበር በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ ክልሎች እየሰራ የሚገኝ ድርጅት ነው። ድርጅቱ ከሩብ ሚሊዮን በላይ መጽሃፍቶችን በመላክ እና ከ130,000 በላይ ህጻናትን በዓመት እያገለገለ ሲሆን ከ70 በላይ ቤተ-መጻሕፍት ማቋቋሙን አስታውቋ...

ሁልጊዜ እራሳችንን እንደ ንጹህ አንይ

 #በጉዞ_ላይ • በተሳፋሪዎች የተሞላዉ አዉቶብስ ጉዞ ላይ ነዉ። ወዲያዉ የአካባቢዉ የአየር ሁኔታ ተቀያየረና አስፈሪ የነጎድጓድና የመብረቅ ብልጭታ መታየት ጀመረ፡፡ ተሳፋሪዎቹ አዉቶብሱ ከአሁን አሁን በመብረቅ ተመታ እያሉ መጨነቅ ጀመሩ መብረቁ ግን መኪናዉን እያለፈ ይወድቅ ነበር፡፡ • እንዲህ አይነቱ አጋጣሚ ሁለት ሶስት ጊዜ እንደቀጠለ ሾፌሩ አዉቶብሱን ከአንድ ዛፍ 50 ጫማ ርቀት ሲቀረዉ አቆመና ተሳፋሪወቹን "ከእናንተ መሃል ዛሬ መሞቱ ግዴታ የሆነ ሰዉ ሥላለ ከአሁን በኋላ አብሮን ከተጓዘ በእሱ ምክንያት ሌሎቻችንም አብረን እንዳንጠፋ ሁላችሁም በየተራ እየወጣችሁ ያንን ዛፍ እየነካችሁ እንድትመለሱ እፈልጋለሁ! መሞት ያለበት ሰዉ ካለም ዛፉን የነካ ጊዜ በመብረቅ ይመታል! ሌሎቻችን ግን እንተርፍለን ማለት ነዉ!!" አለ። ሾፌሩ ይህን ያደረገውም በተለምዶ መብረቅ ዛፍ ላይ ያርፋል ከሚባለው ብሂል ተነሥቶ ነበር። • ሁሉም የመጀመሪያዉን ተሳፋሪ ሄዶ ዛፍን እንዲነካ መጎትጎት ጀመሩ። እሱም እየጨነቀዉና በፍርሃት ተዉጦ ሄዶ ዛፍን ነክቶ በሰላም ተመለሰ። ምንም ሳይሆን በመመለሱም ልቡ በደስታ ጮቤ ረገጠች፡፡ • መጨረሻ ላይ የነበረዉ ተሣፋሪ ተራ እንደደረሰ ሁሉም ሟቹ እሱ እንደሆነ በማሰብ ዐይኑን እያዩት እንዲሄድ ገፋፉት፤ እሱም በመሞት ፍራቻ ተዉጦ ከአዉቶብሱ ወረደ። ከዛፉ ደርሶ እንደነካዉም ኃይለኛ ድምፅ ተሠማ፤ አስፈሪ የመብረቅ ብልጭታም ሆነ። • መብረቁ ግን የመታዉ አዉቶብሱን ነበር። በውስጡ የነበሩት ተሳፋሪዎችም ሞቱ፡፡ እነዚያ ቀደም ብሎ አዉቶብሱን ያለፉት አደጋዎች ሁሉ ያለፉትም በመጨረሻዉ ተሣፋሪ ንጽህና ምክንያት ነበር፡፡                         ...