በወጣትነት ጊዜያችን ስለ ወደፊቱ ብዙም ሳናስብ የተለያዩ ውሳኔዎችን እናደርጋለን። አንዳንድ ጊዜ እነዚህ ውሳኔዎች በመካከለኛ ዕድሜያችን ላይ ክፉኛ ዋጋ ያስከፍሉናል። አንድ ሰው ሲያረጅ ሊጸጸትባቸው ከሚችላቸው ነገሮች መካከል ጥቂቶቹ እነዚህ ናቸው፦
1. ያልተጠቀምንባቸው አጋጣሚዎች
በወጣትነታችሁ ብዙ በሮች ይከፈታሉ፣ ብዙ እድሎች ታገኛላችሁ። ብዙ ወጣቶች በፍርሃት፣ በስንፍና ወይም በትዕቢት ምክንያት እነዚህን አጋጣሚዎች ያልፏቸዋል። ነገር ግን ወጣትነትና ጉልበት እያለ አዲስ ሥራ ለመጀመርና ለራሳችሁ ስም ለመገንባት ምርጡ ጊዜ ነው። አንዳንዶች እድሎቹ ለእነርሱ በጣም ትልቅ እንደሆኑ ያስባሉ። እነዚህን አጋጣሚዎች ተጠቀሙባቸው፤ አለበለዚያ አንድ ቀን ስታረጁ ወደ ኋላ ተመልሳችሁ እነዚያን ያመለጡ እድሎች ለመያዝ ትመኛላችሁ።
2. ያፈረስናቸው ድልድዮች (ያቋረጥናቸው ግንኙነቶች)
በወጣትነት ጊዜያችን ለግንኙነቶች ብዙም አንጨነቅም፤ አብዛኛው ሰው የሚያስበው በማንኛውም ዋጋ ገንዘብ ማግኘትና የስኬት መሰላልን መውጣት ነው። ብዙዎች ለመሻሻል ሲሉ ሰዎችን ይጠቀማሉ ይረግጣሉም፤ ግንኙነቶችን እንደ ቀላል ነገር ይቆጥራሉ፣ ትስስሮችን ያበላሻሉ፣ ለግል ጥቅማቸው ሲሉ ከሰዎች ጋር ይተኛሉ። ነገር ግን እነዚህ መጥፎ ድርጊቶች ወደፊት ዋጋ ያስከፍሏችኋል። ህይወት ያለ ፍቅርና ጓደኞች ምን ያህል ባዶ እንደሆነ ስትገነዘቡ። ስኬታማ ስትሆኑ ነገር ግን በዙሪያችሁ ማንም ሳይኖር ወይም የሚታመን ሰው ስታጡ።
3. ያበላሸነው ሰውነት
በሙሉ ህይወታችሁ የምትኖሩበት አንድ ሰውነት ብቻ ነው ያላችሁ። የምታጨሱት ሲጋራ፣ አብዝታችሁ የምትጠጡት አልኮል፣ የምትወስዱት አደንዛዥ ዕፅ፣ የምትመገቡት ጤናማ ያልሆነ ምግብ፤ ይህ ሁሉ ቀስ በቀስ ያጠፋችኋል። በ50 ዓመታችሁ የአኗኗር ዘይቤ በሽታዎች ሲይዟችሁ፣ በወጣትነታችሁ ሰውነታችሁን ብትንከባከቡት ኖሮ፣ የበለጠ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ብትሰሩ ኖሮ ትመኛላችሁ፤ ነገር ግን ያኔ ጉዳቱ ደርሷል።
4. ያባከንነው ጊዜ
በወጣትነታችሁ በጭንቀት፣ በተሳሳቱ ግንኙነቶች፣ በስንፍና፣ ሶፋ ላይ ተለጥፎ በመዋል፣ ሰበብ በመስጠትና ትርጉም የለሽ ነገሮችን በማሳደድ የምታባክኑትን ጊዜ፤ መቼም አታገኙትም።
5. የቀበርናቸው/ያልተጠቀምንባቸው ተሰጥኦዎችና ህልሞች
በወጣትነታችሁ ተሰጥኦ አላችሁ? ልታደርጓቸው የምትወዷቸውና የተካናችሁባቸው ነገሮች አሉ? እነዚያን ተሰጥኦዎች አዳብሯቸው፣ ተጠቀሙባቸው፣ እንቅፋቶች ቢያጋጥሟችሁም ተስፋ አትቁረጡ፣ በህልሞቻችሁ ተስፋ አትቁረጡ። ተስፋ ከቆረጣችሁ፣ ስታረጁ ከሚወዱት ነገር ጋር ጸንተው የቆዩና ስኬታማ የሆኑ እኩዮቻችሁን አይታችሁ "ይህ እኔ ልሆን እችል ነበር" ብላችሁ ታስባላችሁ። የምትወዱትን ሙያ ተከታተሉ፣ የምትወዱትን የትምህርት መስክ አጥኑ። የማያስደስታችሁን መስክ ውስጥ የህይወታችሁን ዓመታት አታባክኑ።
6. ያጎደፍነው ስም
ስታረጁ፣ ውርስ (legacy) በጣም አስፈላጊ ነው፣ የስማችሁ ዋጋ ወሳኝ ነው። ዝናችሁ ምንድን ነው፣ ምን ትታችሁ ነው የምታልፉት? ብላችሁ ራሳችሁን ትጠይቃላችሁ። ውርሳችሁ ከወጣትነታችሁ ጀምሮ የሰራችኋቸው ድርጊቶች ድምር ውጤት ነው። የህይወት ታሪካችንን የምንጽፈው በየዕለቱ በምንኖረው ህይወት ነው። የሄዳችሁበትን መንገድ መለስ ብላችሁ ስትመለከቱና በራሳችሁ ስም ላይ የወረወራችሁትን ጭቃ፣ የሳባችሁትን ውርደትና ለአለም የጨመራችሁትን ትንሽ ዋጋ ስታዩ፤ ትጸጸታላችሁ።
7. ያመለጠን/ያስከፋነው ጥሩ ፍቅር
በህይወታችሁ ውስጥ በጥሩ ሁኔታ የሚወዳችሁ ታላቅ ሰው አለ? ያንን ሰው አትግፉት፤ አለበለዚያ ያ ሰው ከህይወታችሁ ይወጣል እናም እንደዚህ አይነት አስደናቂ እና በሙሉ ህይወታችሁ የሚስማማችሁን ሰው መቼም አታገኙም። "ከዚያ ሰው ጋር አሁንም ብሆን ኖሮስ?" በሚሉ ሀሳቦች እያረጁ መሄድ ያሰቃያችኋል።
8. የናቅናቸው ወላጆች
በወጣትነት ጊዜ ወላጆችን መናቅ ቀላል ነው፤ ወላጆቻችሁ ምን ያውቃሉ? እነሱ የድሮ ዘመን ሰዎች፣ የማይገቡና ጠባብ አስተሳሰብ ያላቸው ናቸው። ነገር ግን ወላጆቻችሁ ብትስማሙባቸውም ባትስማሙባቸውም፣ የአኗኗር ዘይቤያቸው ምንም ይሁን ምን አሁንም ወላጆቻችሁ ናቸው። ወላጆቻችሁ ሳይሞቱ ወይም ከእናንተ ተለይተው ሳያረጁ አትተዋቸው፣ ታረቁ እና ተስማሙ። ስታረጁ፣ ወላጆቻችሁ ለምን ወደ እናንተ መቅረብ እንደፈለጉ ትገነዘባላችሁ። ዕድሜያችሁ በጨመረ ቁጥር ዋጋቸውን የበለጠ ትረዳላችሁ።
የእህትን ወይም የወንድምን ዋጋ ለማወቅ
የሌለውን ሰው ጠይቁ።
የአስር ዓመትን ዋጋ ለማወቅ፦
አዲስ የተፋቱ ጥንዶችን ጠይቁ።
የአራት ዓመትን ዋጋ ለማወቅ፦
ተመራቂን ጠይቁ።
የአንድ ዓመትን ዋጋ ለማወቅ፦
የማጠቃለያ ፈተና የወደቀ ተማሪን ጠይቁ።
የዘጠኝ ወርን ዋጋ ለማወቅ፦
በሞት ና በህይወት መካከል የተወለደ ልጅን የወለደች እናትን ጠይቁ።
የአንድ ወርን ዋጋ ለማወቅ፦
ወሩ ሳይደርስ የተወለደ ልጅ የወለደች እናትን ጠይቁ።
የአንድ ሳምንትን ዋጋ ለማወቅ፦
የሳምንታዊ ጋዜጣ አዘጋጅን ጠይቁ።
የአንድ ደቂቃን ዋጋ ለማወቅ፦
ባቡር፣ አውቶቡስ ወይም አውሮፕላን ያመለጠውን ሰው ጠይቁ።
የአንድ ሰከንድን ዋጋ ለማወቅ፦
ከአደጋ የተረፈን ሰው ጠይቁ።
አሁንም የአንድ ሰከንድን ዋጋ ለማወቅ፦
ኃይሌን ወይም ቀነኒሳን ወይንም ቦልትን ጠይቁ።
ጊዜ ማንንም አይጠብቅም።
ያላችሁን እያንዳንዱን ቅጽበት ዋጋ ስጡት።
@yeshanehtube
Comments
Post a Comment