ክፉ መሆን ክፋት ነው ።ደግ መሆን ግን ደግነት አይደለም ። ሰውነት ነው ። የተፈጠርነው ከደግ አምላክ እስከሆነ ድረስ ደግ ልንሆን ነው ። ብዙዎቻችን በክፋት ቦታ ላይ ስለታየን ደጎች ሲገኙ ፃድቅ ይሆኑብናል ። ግን ደግነት ተፈጥሯችን ነው ። ደግ ልንሆን ፣ ለሌሎች ልንሆን ነው የተፈጠርነው ። ክፋትን እንድናደርግ አልመጣንም ። አንዳችን ለሌላችን ተባባሪ ፣ ደጋፊ ስንሆን እንደተፈጥሯችን መሆን እንጂ የተለየ ሰውነት አይደለም ። ሌሎችን የምናግዘው፣ የምንተባበረው ፣ የምንረዳው ደግሞ ወደንና ደግ ሆነን ሳይሆን እኛም ያለሌሎች እገዛ ሰው መሆን ስለማንችል ነው ። ሰው የሆነው ራሱ በሰው ነው ። ሁሉ ነገራችን ፣ ተፈጥሯችን ፣ ደምና አጥንታችን ራሱ ከሌሎች የተውጣጣ ነው ። እዚህ የደረስነው በሌሎች እገዛ ነው ። ለሌሎች የምንሆነው ሌሎች ስለሆኑልን ነው ። ሌሎችን የምናኖረው በሌሎች ስለኖርን ነው ። እኛ የራሳችን ሳንሆን የሌሎች መዋጮ ነን ። ክፋት ስናደርግ " ክፉ " የምንባለው ተፈጥሯችን የክፋት ስላልሆነ ነው ። ከተፈጠርንበት ዓላማ ስለወጣን ነው ። ትዕዛዝ ስለተላለፍን ነው ። መልካምነት ግን የተፈጠርንበትን ዓላማ ማስፈፀም ነው ። በቃ ሌላ አይመስለኝም ። ከሰውነት አለመጉደል ነው።
Prepared by: Yeshaneh Adimasu (Lecturer at Adama Science and Technology Uuniversity) "Together We Can" There are #200 multiple questions which is very helpful for all grades, especially for Grade 12 students around every corner of Ethiopia. Th questions are prepared based on the New curriculum from Grade 11 (unit 1-3) and 12 (unit 1&2) and old curriculum from Grade 9 (Unit 1-3) and 10 (Unit 1) Those who have interest to access the video lectures from Grade 9, 10, 11, and 12, please visit my YouTube channel "Yeshaneh Tube" on the link: https://www.youtube.com/@yeshanehtube Further more; If you have any comment and suggestion please write on the comment section @yeshanehtube DO carefully !! Good luck Instruction: Choose the correct answer from the given alternatives 1. ...
Comments
Post a Comment